Abu_Oubeida~channel


Kanal geosi va tili: Eron, Forscha


من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم
{ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Eron, Forscha
Statistika
Postlar filtri






(فَبِظُلْمٍ مِّنَ الَّذِينَ هَادُوا حَرَّمْنَا عَلَيْهِمْ طَيِّبَاتٍ أُحِلَّتْ لَهُمْ)

(በአይሁዶችም በደል በእነርሱ ላይ የተፈቀደላቸውን ከመልካም ነገር እርም አደረግንባቸው)።

አለመታዘዝ የእጦት ምክንያት ነው።




እዚህ የኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ፅሁፍ ኮመንት ያደረገው የዚህ አካውንት ባለቤት ነው።

Bio: ላይ የጻፈው/ቺውን ተመልከቱ፡ድሮም "ጀህል ደፋር ያደርጋል" አሉ።ለካ እውነት ነው።አለ አንዳች ተጨባጭ ነገር እያመጡ እንደማስቲካ የሚለጥፉት ነገር እንደው ትንሽ እንኳን አያሳፍራቸውም? ሲ ልጃቸውን ገንዘቧን ቀምቶ ፈቶባቸዋል እንዴ? ምን ጉዶች ናቸው በአላህ።ውሸት ምን ያክል ቢቀላቸው ነው እያነሱ የሚለጥፉበት? ሲ አላህ ዘንድ እንደሚተሳሰባቸው አያውቁም እንዴ? ሰው ቢያንስ ረድ አቁመኻል ብሎ ቢከስ እንኳን እሺ ይሁን ይባል።ጪራሽ ዲፋእ አድርገኻል ብዙ ሰው እንዴት ባልዋለበት ይከሰሳል?!ይሄን የምቀኝነት እሳታችሁን አላህ ያጥፋላችሁ ሌላ የምለው የለኝም።

የቴሌግራም ቻነል፦
t.me/AbuOubeida


“ እናቴን በሕይወት ባጣም ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እናቶቼ ያላችሁን በማገዝ ከሞት ታደጉኝ ” - የ16 ዓመቷ የልብ ታማሚ

በጸጥታ ችግር ከወለጋ ተፈናቅላ በደብረ ብርሃን ቻይና መጠለያ ካምፕ ከገባች አራት አመት እንዳስቆጠረች የገለጸችው የ16 ዓመት ታዳጊ ለቀዶ ጥገና ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቋ እርዳታ እንዲረግላት ተማጸነች።

በቶሎ ካልታከመች ሕይወቷ ከባድ አደጋ ላይ መሆኑን እንደተነገራት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሏን የሰጠችው ታዳጊዋ፣ ለህክምናው ወጪ 783 ሺሕ ብር እንደተጠየቀች፣ ገንዘቡን ማግኘት እንዳልቻለች አስረድታለች።

“እናቴ ሞታለች። የወለጋ ተፈናቃይ ነኝ። ሀኪም ‘የልብሽ የደም ማስተላለፊያ አብጧል’ አለኝ” ያለችው ታማሚዋ፣ በሕይወት ያሉት ቤተሰቦቿም በጸጥታው ችግር ቤት ንብረታቸውን ትተው ተፈናቃይ መሆናቸውን ተናግራለች።

እርዳታ ጠያቂዋ ታዳጊ ሀያት በላይ፣ “እናቴን በሕይወት ባጣም ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እናቶቼ ያላችሁን በማገዝ ከሞት ታደጉኝ” ስትል ተማጽናለች።

የታማሚዋ ቤተሰቦችም፣ ታዳጊ ሀያት ህመሙ ከጀመራት ሰባት አመታትን እንዳስቆጠረች፣ በቻሉት መጠን ህክምና እየተከታተለች ብትቆይም መፍትሄ ሳታገኝ እንደቆየች ገልጸው፣ ልበ ቀናዎች እንዲረዷቸው ጠይቀዋል።

መርዳት ለምትሹ፣ 1000628382895 የታማሚዋ እህት ፋጡማ አሊ ሁሴን የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ነው።

ደውሎ ለመጠየቅ፣ በ
0945667806 ታማሚዋን፣ በ0921195123 ወንድሟን፣ 0955581772 እህቷን ፋጡማ አሊን ማግኘት ይቻላል።

@tikvahethiopia


መቆሚያ ያጣው የመርከዙ የቁልቁለት ጉዞ!
~
የሸሪዐ ቀዳሚ ግብ ጉዳትን ማስወገድ፣ ካልሆነ መቀነስ እንዲሁም ጥቅምን ማስገኘት ነው። አንዳንዴ የከፋውን ሸር ለማለፍ ወይም ለመቀነስ ሲባል ያነሰውን ሸር እንፈፅም ዘንድ ጫና ሊገጥመን ይችላል። በዚህ የተነሳ ለአጠቃላዩ የደዕዋ መስለሐ ሲባል ውስጣችን የማያምንበት ጉዳይ ላይ ልንነካካ እንችላለን። ይሄ ብስለት አልፎም ድፍረት የሚፈልግ ጉዳይ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ ከእለት ወደ እለት መንሸራተቱን በ "መስለሐ" ወረቀት እየጠቀለለ የሚያቀርብ ብኩን አለ። ማዶ ላይ ያለን "መስለሐ" ሲያስብ ዙሪያውን ስላለው ተጨባጭ አያስብም። "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደሚባለው ማለት ነው።

የመርከዝ ኢብኑ መስዑድ አካሄድ እዚህ ላይ ነው ያለው። መሪዎቻቸው በዑጅበ ነፍስ የተወጠሩ፣ ቀድራቸውን የማያውቁ፣ "ከኛ ወዲያ መስለሐ እና መፍሰዳ የሚለይ ላሳር" ውስጥ የገቡ ናቸው። ይሄ አዲስ የመጣ ሳይሆን ነባር አመላቸው ነው። በዙሪያቸው ያለው "አገር ለመምራት እድሉ ቢስሰጣቸው መምራት የሚያስችል ብቃት አላቸው" የሚል፣ ቢያጥፉት የሚታጠፍ፣ ቢዘረጉት የሚዘረጋ እንዳሻቸው የሚሰሩት ስብስብ ለራሳቸው የተሳሳተ ግምት እንዲይዙ አድርጓቸዋል። የፈለገ ቢወርዱ "ኧረ አሁንስ በዛ!" የሚል ድፍረት ያለው ከኖረ ከስንት አንድ ነው። እሱውም ከተገኘ። ሰው በዚህ መጠን እንዴት በጋራ ጭፍን ተከታይ ይሆናል? የሚገርም ነው!

ወላሂ! መርከዙን የምታድኑት ኢኽላስን መሰረት ባደረገ እውነተኛ አካሄድ እንጂ በጭፍን ውግንና አይደለም። ሰዎቹንም ሲያጠፉ እጃቸውን በመያዝ እንጂ በጭፍን ብትከላከሉ እነሱንም ላትጠቅሙ ራሳችሁንም ትጎዳላችሁ። ይልቁንም ከዚህ "እናንተን የማይታያችሁ ይታየናል" ከሚል አጉል ግብዝነት እንዲወጡ ብታግዟቸው ነው የሚሻለው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


የበረታችሁ ሰዎች የኸይር ስራ ላመላክታችሁ፦የማውቃቸው 3ት ሚስኪኖች አሉ የምትበረቱ ከሆነ ለረመዷናቸው ለአንዳንድ ነገር የሚሆን አበርክቱላቸው።ሁለቱ አካላቶች በየረመዷኑ መጨረሻ ላይ የሶደቀተል ፊጥር እህል በመሰብሰብ ከማደርስላቸው ሰዎች መካከል ናቸው።እና ለመተባበር ከፈለጋችሁ ከስር ባለው ቦት ጻፉልኝ አካውንት እሰጣችኋለሁ።
#ቦት @AbuOubeida90_bot

ማንቂያ፦ ሰዎቹን በ3ት ያሳጠርኳቸውና አካውንት በዚህ ያለጠፍኩት፡ብዙ ሰው ላለመሳስቸገር ነው።እንጂ በርትቶ ጠቅም አድርጎ የሚልክ ካለ፡እንደሚበቃ አድርጌ ተጨማሪ ሰዎችን አካትታለሁ።


የተበዳዮች እንባ፡በአይኖቻቸው ላይ ስትታይ እርሷ ፈሳሽ ውሃ ብቻ ናት።ነገር ግን እርሷ ከአላህ ዘንድ በዳዮችን የሚመታባት የሆነች #መብረቅ ናት።


የቁርአን ነገር ይገርመኛል፡በቃ በቀራሃው ቁጥር ለውስጥህ ሰላምን ይለግስሃል፤መረጋጋትን ታገኛለህ፤የሆነ ደስስ የሚል ስሜት በውስጥህ ይንሸራሸራል።በቃ ከርሱ እንዳትርቅ የሚያደርግ ነገር አለው።

#እርሱ_የጌታዮዬ ንግግር ነው

አቡ ኡበይዳ
t.me/AbuOubeida


የነሲህ ቲቪ አመራሮችና ኡስታዞች አፍሪካ ቲቪን ጎበኙ

የተወዳጁ ነሲህ ቲቪ አመራሮችና ኡስታዞች  ጁምዓ፣ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ል የአፍሪካ ቲቪን ስቱዲዮ ጎብኝተዋል።

የነሲህ ቲቪ ስራ አስኪያጅ ዓብዱረሺድና በቲቪው በተለያዩ የስራ ዘርፎች ላይ የሚሰሩ ኡስታዞችና ባለሙያዎች በጉብኝቱ ተሳትፈዋል።

በአፍሪካ ቲቪ የበላይ ጠባቂ የሆኑት ታላቁ ዓሊም ሼህ ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን እና የአፍሪካ ቲቪ ዋና ስራ አስኪያጅ ኡስማን ሁልው የቲቪው አመራሮች ጋር በመሆን ለንግዶቹ አቀባበል እድርገውላቸዋል።።

በጉብኝታቸው ሁለቱ ቲቪዎች በጋሩ ሊሰሮባቸው በሚችሉባቸው በርካታ ስራዎች ላይም አብረው መስራት እንደሚችሉ እና ሊተጋገዙባቸው በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መክረዋል ።
______
ትልቅ ተቋም በዚህ
ልክ ሲወድቅ ያሳዝናል።ንጹሁን የሰለፍያን ደእዋ በዚህ ልክ መካድ ለጤነኛ ሰው በጣም ያማል።ላስተዋለው ይከብዳል።ይሄ በዳእዋውም ላይ ሆነ ባመነ ህዝብ ላይ የተሰራ  ነውር ነው።ትልቅ ነውር። በእርግጥ የሰዎች ልቦና #በሃያሉ ጌታ ጣቶች መካከል ናት።እንዳሻው ይገለባብጣታል።ለዚህም ነበር የአላህ መልእክተኛው አለይሂ ሶላቱ ወስሰላም፡አንተ ልቦናን ገለባባጭ የሆንከው ጌታ ሆይ ልቤን በእምነትህ ላይ አጽናልኝ የሚሉት።እውነትም ጽናትን መጠየቅ ያስፈልጋል።አላህ የውስጥ ማያቸውን ይክፈትላቸው ከማለት ውጪ ምን ይባላል¿!

የቴሌግራም ቻነል፦
t.me/AbuOubeida


ኹዝ ዓቂደተክ.apk
166.8Mb
🆕📲አድስ አፕሊኬሽን ተለቀቀ

📖 ኹዝ _ ዓቂ^ደተክ
ሚነ'ል _ ኪታቢ
ወስ' _ ሱነ^ህ
📖

🛜🏢 በአህሉል አሰር የሴቶች መድረሳ የተሰጠ ሙሉ ደርስ

🎙በአቡ ዒምራን
https://t.me/Abu_lmran_Alaseriy


እረመዳን መምጣቱን አስመልክቷ የተዘጋጀ ታላቅ የዳእዋ ዲግስ

         

ተጋባዥ ኡስታዞች


👉📢ኡስታዝ ኢብኑ ኸይሩ ከሱእዲ

👉🎧📢ኡስታዝ ዓብደሽኩር  ከአሶሳ

👉🎧📢በኡስታዝ አበ ሂበቲላህ  ከደሴ

👉🎧📢ኡስታዝ አቡ ሉቅማን ሁሴን

👉📢ኡስታዝ አቡ ዒምራን አጃኢቡ 

👉🎧📢ወንዲም አቡ ዑሰይሚይን  ከደቡብ

👉🎧📢ወንዲም ኑረዲን አል አረብ  ከሱእዲ

        
የቁራአን ግብዣ

💫🎤ቃሪእ አቡ ዘይድ ኻሊድ ከየመን

💫🎤ቃሪእ አቡ ረያን አብደረህማን  ከኮንቦልቻ

💫🎤ቃሪእ አቡ ዑበይዳ ሲራጅ ከአድስ አበባ

💫🎤ቃሪእ አቡ ሙስሊም ሀቢብ ከኮንቦልቻ

የፕሮግራም መሪና አስተባባሪ ወንዲም አቡ ሀሣን


በሀላል የኦላይን ገባይ ማአከል  የተዘጋጀ 

እለተ ማክሰኞ ምሽት ሊኩን ለሌሎችሸር  በማድረግ በቅርብ እርቀት ይጠብቁን !!

በኢትዩ ከምሽቱ  3:00 ሰዓት
በሳኡድ.ከምሽቱ 9:00 ሰዓት
በዱባይ ከምሽቱ  10:00 ሰዓት


ፕሮ ግራሙ የሚተላለፍበት ሊንክ➴➴➴➴➴
          https://t.me/Hewditu
https://t.me/Hewditu
                   https://t.me/Hewditu


ከሚረክሱ ሰዎች ውስጥ፦እዛም እዚህም የሚያበዙና የማይመለከታቸው ውስጥ የሚገቡ ናቸው።እናንተ የሌላችሁበት ስራ ሁሉ የማይሳካ የሚመስላችሁ ሰዎች ግን ሰላም ነው!!


ምን ሁኖ ይሆን፡ምናልባት ለማለት የፈለኩትን ሳይረዳኝ ቀርቶ ተቀይሞ ይሆን?ወይስ ሰዎች አሳስተው ነገሩት?ምናልባት የራቀው የተቀየምኩ መስሎት ይሆን የሚሉ ከቅን ሰዎች ውስጥ ያሉ ቅን ልቦች አሉ።ይሄ የመልካምነታቸው ማሳያ፡የደግነታቸው ምልክት ነው።ግና ምን ያደርጋል እነርሱ እንዲህ ይጨነቃሉ ሰው ግን አይረዳቸውም።ይባስ ብሎ ባልገባው በመተርጎም በክፋት ይከሳቸዋል።

አቡ ኡበይዳ
t.me/AbuOubeida


አሁን በኡስታዝ ኸድር አሕመድ እየተሰጠ

ያለ ኮርስ ገብታችሁ ተከታተሉ…

https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group?livestream=c21006480a441f1254


ታላቅ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም      
           በቡታጅራ ከተማ!

=
እነሆ የፊታችን ሐሙስ ቀን 06/06/2017 ከመግሪብ ሰላት በኋላ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ቀን 08/06/2017 ድረስ የሚቆይ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም በቡታጅራ ተሰናድቶ ይጠብቅዎታል።

በዕለተ እሁድ ደግሞ ሰፋ ባለ መልኩ በኢንሴኖ ከተማ ደማቅ ፕሮግራም የሚካሄድ ይሆናል። በዚህ ፕሮግራም የተለያዩ ጊዜውን ያማከሉ አርእስቶችና ረሳኢል በኮርስና ዳዕዋ መልክ ይሰጣሉ።

እርሶም የዚህ ታላቅ ፕሮግራም ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጥሪ ስናቀርብልዎ በታላቅ ደስታ ነው።

☞ ተጋባዥ እንግዶች፦
     * ሸይኽ አወል አሕመድ አልከሚሴ
     * ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አልከሚሴ እና ሌሎችም ኡስታዞችና ዱዓት ይገኛሉ።

«እውቀትን ፍለጋ መንገድን የጀመረ አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል።» ረሱልﷺ

https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group


እህታችን አፋልጉን ቤተሰቦቿ!!


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

     🎊 ልዩ የዳዕዋና የኒያ ፕሮግራም
🎉

በመርከዝ ኢብኑ ዐባስ ኢስላሚክ ሴንተር «ማስተባበሪያ ግሩፕ» ላይ በአሏህ ፈቃድ
ነገ ጁሙዓ ማታ  3:00 ጀምሮ


     ↷🔊ተጋባዥ እንግዶቻችን↷

➊ ሸይኽ አወል አሕመድ አል_ኬሚሴ"ሐፊዘሁላህ"
      
❷➻ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ኬሚሴ  "ሐፊዘሁላህ"
  
❸➻ ኡስታዝ አቡ አብደላህ (ሷዲቅ ኢብኑ ኸይሩ "ሐፊዘሁሏህ"

❹ ወንድም አቡ ሐሳን አሊይ ዩሱፍ ሐፊዘሁሏህ


ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም ኢንሻአላህ ይኖራሉ።


የፕሮግራም መሪ እና አስተባባሪ
    ➠ ወንድማችን አቡ ዑበይዳ ከኼሚሴ
➠ አቡ ማሒ ኢብኑ ኢድሪስ

  
   በዚህ ልዩ ፕሮግራም ላይ አይደለም መቅረት ማርፈድ አይታሰብም  የተጀመረውን  የኢብኑ አባስ መረከዝ  ለማስጨረስ ልዩ እና ያማረ  የደመቀ የንያ ፕሮግራም እንዲሁም አሁን የደረሰበትን ጉዳይም እዚያው የምንሰማ ይሆናል  ኢንሻ አሏህ እንዳትቀሩ ሁላችሁም እስከነ ቤተሰቦቻችሁ ተጋብዛችኋል ስላችሁ....

       ማሳሰቢያ
ጁመአ ምሽቱን የምናሳልፈው ከኢብኑ አባስ መርከዝ ጋር ነው።  ተናግሪያለሁ።


መቅረት አይደለም ማርፈድ አይታሰብም!

🔍 ስርጭቱ የሚተላለፍበት ግሩፕ ሊንክ
                            
╰┈➢
t.me/+lmLw2jJXwF45Zjdk

🛎انشر تؤجر !
        🔑 كن مفتاحا للخير
               الدال على الخير كفاعله🏝


https://t.me/+lmLw2jJXwF45Zjdk


ደዕዋ ላይ ለተሰማራችሁ ሁሉ!
~
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الْإِيمَانِ "
"ከናንተ መጥፎን ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው። ካልቻለ በምላሱ፤ ካልቻለ ደግሞ በልቡ። ይሄኛው የመጨረሻ ደካማው እምነት ነው።" [ሙስሊም: 186]

ስለዚህ ያዩትን መጥፎ ነገር ማስወገድ ኢስላማዊ ኃላፊነት ነው። ቀጥታ ማስወገድ ካልተቻለ በቃል ወይም በፅሁፍ መናገር ይገባል። ይሄ ጉዳይ የሁሉም ሙስሊም ግዴታ ቢሆንም የዱዓት ኃላፊነት ግን ከሌሎች የከበደ ነው። ስለዚህ በሃገር በአካባቢያችሁ የሚታዩ ችግሮች ላይ እርምት መስጠት ይገባል። ሁሉም በዝምታ ከተሰማማ ጥፋቱ 'ኖርማል' እየተደረገ ይያዛል።

ባይሆን ሁለት ነገሮችን ማስተዋል ጥሩ ነው።

1ኛ፦ ባደባባይ የሚፈፀሙ ጥፋቶችን ወይም አሳሳች ስብከቶችን ማረም የነፍስ ወከፍ ሳይሆን የጋራ ግዴታ ነው፣ ፈርዶል ኪፋያ። ስለዚህ ከፊሎች ይህንን ኃላፊነት ከተወጡ ሌሎች ከተጠያቂነት ይድናሉ። ስለዚህ በንዲህ አይነት ሁኔታ ያልተናገረውን ሁሉ ወንጀለኛ ማድረግ አይቻልም።

2ኛ፦ ያያችሁትን ጥፋት ስታስጠነቅቁ በራሳችሁም ይሁን በደዕዋችሁ ላይ የባሰ ጥፋት የሚከተል ከሆነ በመጀመሪያ ግራ ቀኝ ማየት ይገባል። አጥፊዎች ጉልበት ያላቸውና የተደራጁ በመሆናቸው የተነሳ አንድ ጥፋት ላይ ስትናገሩ ደዕዋችሁን በእጅጉ በሚጎዳ መልኩ የሚያሰናክሏችሁ ከሆነ ለተሻለው ጥቅም ስትሉ ለጊዜው ዝቅ ብላችሁ አሳልፉት።

ብትናገሩ ምን ሊከተል እንደሚችል እየገመታችሁ ሳለ ነገር ግን በቡድናዊ ልዩነት ተነሳስቶ ወይም በእልህ ተገፋፍቶ "ዛሬውኑ ካልጮሃችሁ" ብሎ ለሚጫናችሁ አካል እጅ ሰጥታችሁ ብትናገሩ ይሄ ኢኽላስ ሳይሆን ይዩልኝ፣ ይስሙልኝ ነው የሚሆነው። ይሄ ደግሞ ሺርክ እንደሆነ እንዳትረሱ! በዚህ መልኩ በመናገራችሁ መስጂዳችሁን ብትነጠቁ ወይም ደዕዋችሁ ቢሰናከል ድርብርብ ወንጀለኛ ትሆናላችሁ። እጅ ጠምዝዘው ያለ ጊዜው እንድትናገሩ ሊያስገድዷችሁ የሚሞክሩ አካላትንም አታስደስቱም። ስለዚህ ከመነሻው በሚገባ መዝናችሁ ተናገሩ። ባይሆን በቦታው መናገር ሲጠበቅባችሁ ጊዜ ፍርሃታችሁን በ 'መስለሓ' ስም እየሸፈናችሁ ራሳችሁን እንዳትሸውዱ። አስተውሉ! ፍርሃት ለራስ ሲሆን ጥንቃቄ ነው ስሙ፡፡ የፈሪዎች ሂሳብ!

አንድ ነገር ግን እንዳይዘነጋ። 'መስለሓ' እና 'መፍሰዳ'ን በመገመት ላይ የሰዎች እይታ የሚለያይበት ብዙ አጋጣሚ አለ። በዚህን ጊዜ ሰዎችን ልባቸውን ለአላህ በመተው የታያቸውን ነገር በኢኽላስ እንዲያደርጉ መተው ይገባል። በመሰል ሁኔታዎች ላይ መናገሩ የተሻለ ሆኖ የታየው አካል ይናገር። በመናገሩ የከፋ ነገር ይከተላል የሚል ስጋት ያለው ዝም ይበል። በ'ንዲህ አይነት ሁኔታ ላይ አንዱ ሌላውን በራሱ ሃሳብ ሊያስገድድም ሊወነጅልም አይችልም። ያለበለዚያ የሚቀረው ምርጫ መናቆርና መለያየት ብቻ ነው። ከዚያ መሬት ላይ ከሚታየው ጥፋት ይልቅ በጎንዮሽ ልፊያ መጠመድ ይከተላል።

ብልጥ ማለት አላህ ማስተዋልን ያደለው ነው። አስፈላጊ ሲሆን የወቃሽን ወቀሳ ሳይፈራ ጀግና የሚሆን፣ የጥፋት ኃይሎችን እስከ ጥግ በድፍረት የሚጋፈጥ። መጋፈጡ የባሰ ጣጣ እንደሚያስከትል ሲያምን ደግሞ ስሜቱን የሚቆጣጠር፤ ራሱን የሚያሸንፍ፤ የራሱን ሃሳብ ሌሎች ላይ ካልጫንኩ ብሎ ሁከት የማይፈጥር። አላህ ማስተዋሉን ያድለን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.